Monday, September 21, 2015

‹‹የመንግሥት አመራር በሙሉ ሙስና ስለፈጸመ ስብስብ አድርጋችሁ የምታደርጉትን አድርጉ የሚል መልዕክት አልደረሰኝም››

ባለፈው ዓርብ መስከረም 7 ቀን 2008 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽነር አቶ ዓሊ ሱሌይማን፣ ከጋዜጠኞች ከተነሱላቸው ጥያቄዎች መካከል አንዱ መንግሥታዊው ሥርዓት በሙስና ውስጥ
መዘፈቁን በግልጽ እየተናገረ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ግን በመናኛ ጉዳዮች ላይ አተኩሯል የሚል ነው፡፡ የፖለቲካና የሕግ ቋንቋ የተለያዩ መሆናቸውን የተናገሩት አቶ ዓሊ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዕርምጃ የሚወስደው በማስረጃ ላይ ተመሥርቶ ነው በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ ጉባዔ ወቅት በሙስና ላይ ቁርጠኛ የሆነ አመራር አለመሰጠቱና ሙስናን መታገል አለመቻሉ ቢገለጽም፣ እከሌ ሙሰኛ ነው ተብሎ መረጃ ባለመቅረቡ ወደ ሕግ ለመሄድ አይቻልም ብለዋል፡፡ መንግሥት አሁንም ሙስናን ለመታገል ቁርጠኛ መሆኑንና እሳቸውም የተረዱት በዚህ መንገድ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ‹‹የመንግሥት አመራር በሙሉ ሙስና ስለፈጸመ ስብስብ አድርጋችሁ የምታደርጉትን አድርጉ የሚል መልዕክት አልደረሰኝም፤›› ያሉት አቶ ዓሊ፣ ከሙስና ጋር በተያያዘ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች የሰጡዋቸው ምላሾች በ ቢዝነስና ኢኮኖሚ ገጽ ላይ ተስተናግደዋል፡፡

ምንጭ:http://www.ethiopianreporter.com

No comments:

Post a Comment