Monday, September 21, 2015

እኛና ስልካችን


ሰሚት አካባቢ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡ ጊዜው ሕፃን አዋቂ ሳይባል በርካታ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች በሚጾሙት ፍልሰታ ጾም ወቅት ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያኑ መቅደስ የተገኙት ምእመናን የቅዳሴ መጀመርን ይጠባበቃሉ፡፡
አንዳንዶቹ በፀጥታና በዝምታ ተቀምጠዋል፡፡ ፀሎት የሚያደርጉም አሉ፡፡ በሠላሳዎቹ መጨረሻ እንደምትሆን የገመቷት ወጣት ሁኔታ እንዳስገረማቸው አጠገቧ የነበሩት እናት ይናገራሉ፡፡ ወጣቷ ቤተ መቅደስ ገብታ ከተቀመጠች ጀምሮ እጇና ዓይኗ ከስልኳ አልተለዩም፡፡ አንዴም ቀና ሳትል በዚህ ሁኔታ ረዥም ደቂቃዎችን አሳለፈች፡፡ ቅዳሴ ተጀመረ ተጋመሰም፡፡ ወጣቷ ቅዳሴ ሲጀመር ያስቀመጠችውን ሞባይል ስልኳን አንስታ ከፍ አድርጋ በመያዝ ፀሎት እንደሚያደርግ ሰው ሁሉ አሁንም አሁንም ትሰግዳለች፡፡ ልጅቷን በመገረም ሲከታተሉ የነበሩት እናት ወዲያው በስልኳ የፀሎት መጽሐፍ እያነበበች እንደሆነ ተረዱ፡፡
ታክሲ ላይ፣ ካፍቴሪያ፣ በስበሰባ አዳራሽ ሌላም ሌላም ቦታ ላይ አንድ ጠረጴዛ ተጋርተው ተጠጋግተው የተቀመጡ ጓደኛሞች እንኳ እርስ በርስ ከመጫወት ይልቅ ስልካቸውን መርጠው በስልክ ሲጠመዱ መመልከት የተለመደ እየሆነ ነው፡፡ ሁኔታው ሰዎች ከመቼውም በላይ ስልካቸውን የመረጡበት ጊዜ ነው ለማለት የሚያስደፍር ብዙ ነገሮችን ማንሳት ይቻላል፡፡
ሰብሰብ ብለው ሻይ ቡና እያሉ፣ ለማስተዛዘን ከለቅሶ ቤት ተገኝተው፣ የቤተሰብ እራት ላይ፣ ስብሰባ ላይ ወይም ክፍል ውስጥ ሰዎች መልዕክት በመላክ ወይም በመመለስ፣ ማኅበራዊ ድረ ገጾችን በመመልከት፣ ፎቶ በማንሳት አልያም በመነሳት መጠመድ በብዛት እየተስተዋለ ያለ ትዕይንት ነው፡፡ ጥቂት የማይባሉ ስልካቸው ድምፅ አሰማም አላሰማም የትም ይሁኑ የት አሁንም አሁንም ስልካቸውን እያወጡ መመልከት ልምድ የሆነባቸው ይመስላል፡፡ ምንም ነገር እንዳያመልጠኝ በሚል ጥንቃቄ ወይም አንዳንድ ነገሮች፣ ኦን ላይን ያሉ ወዳጆች ቢያመልጡኝስ በሚል ሥጋት በማንኛውም ሰዓት የስልካቸውን ኢንተርኔት ኦን አድርገው የሚንቀሳቀሱም አጋጥመውናል፡፡
በሠላሳዎቹ አጋማሽ የሚገኝ ወጣት ነው፡፡ በአንድ የግል ተቋም ውስጥ ኤክስፐርት ነው፡፡ ሁልጊዜም ስልኩ ኦን መሆኑን በተደጋጋሚም ስልኩን እንደሚመለከት ይናገራል፡፡ በተለይም ኢንተርኔቱን ክፍት የሚያደርገው ማኅበራዊ ድረ ገፆች ላይ የሚወጡ ነገሮች እንዲያመልጡት ስለማይፈልግ፤ ኦንላየን ከሚያገኛቸው ጓደኞቹ ጋርም ማውራት (ቻት ማድረግ) ስለሚፈልግ እንደሆነ ይገልጻል፡፡
‹‹ከጓደኞቼ ጋር ምሳ ልበላ ቁጭ ብዬ ስልኬን ዓየት ላደርግ እችላለሁ ግን ሳልቆይ ቶሎ አስቀምጣለሁኝ፡፡ ቤትም ሌላ ቦታም ስልኬን አየት አደርጋለሁኝ ግን ብዙ አልቆይም›› ይላል፡፡ እሱ እንደሚለው በቀን የሀምሳ ወይም የመቶ ብር ካርድ የሚጨርስ ቢሆንም ይህን እንደ ችግር አይቆጥረውም፡፡ ምክንያቱም ከጓደኞቹ ጋር ቻት ማድረጉንና ማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይ የሚወጡ ነገሮችን መከታተሉን እንደ ትልቅ ነገር ይመለከተዋል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይም የብዙዎችን ስማርት ፎን መያዝ ተከትሎ ሰዎች ሁሉ ነገራቸው ከስልካቸው ጋር እየሆነ መሆኑን መታዘባቸውን ይናገራሉ አቶ ጌትነት አማረ፡፡ በአንድ መንግሥታዊ ባልሆነ ድርጅት ውስጥ የትምህር ጥናትና ምርምር ኤክስፐርት ናቸው፡፡ ‹‹ሻይ ቡና ለማለት ከጓደኛው ጋር ቁጭ ብሎ አጠገቡ ያለውን ጓደኛውን ትቶ አሜሪካ ወይም አውሮፓ ካለ ጓደኛው ጋር ቻት የሚያደርግ ብዙ ሰው አለ፡፡›› የሚሉት አቶ ጌትነት፣ በእንዲህ ያለ ሁኔታ ውስጥ አብሮ ያለው ሰው እንዴት ስልኩ ላይ ከተጠመደው ሰው ጋር ሊያወራ ሊጫወትስ ይችላል? ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡ የዚህ ዓይነቱ ሁኔታ የራሳቸውን ቤተሰብ ጨምሮ በቤት ውስጥ፣ ቢሮና ሌሎችም ቦታዎች ላይ ዕለት በዕለት እየታየ እንዳለ በመግለጽ የባሰ ያሉትን አጋጣሚ ያስታውሳሉ፡፡
ስብሰባ ላይ ነው፡፡ ጥናቷን በፕሮጀክተር በማቅረብ ላይ ያለችው ባለሙያ ጥያቄ ወይም አስተያየት ካለ ጠይቃ አሁንም አሁንም ስልኳ ወዳለበት ጥግ ሔደት እያለች ስልኳን ትመለከታለች፡፡ አንዴ ሁለቴ እንጂ አትደጋግመውም ብለው አሰቡ ታዳሚዎቹ፡፡ አቅራቢዋ ግን መለስ መለስ እያለች ስልኳን መነካካቷን ቀጠለች፡፡ ነገሩ የገረማቸው የሻይ ዕረፍት ላይ ለምን እንደዚያ እንደምታደርግ ጠየቋት፡፡ ከጠየቋት መካከል እሳቸው አንዱ ነበሩ፡፡
የአቅራቢዋ መልስ ‹‹ስልኬን በተደጋጋሚ መመልከቴ እኔን ምንም አይረብሸኝም እናንተም የምትሰጡትን አስተያየት በደንብ ነው የምከታተለው›› የሚል ነበር፡፡ እሷ ብቻ ሳትሆን ከሰው መካከል ሆነው በስልካቸው የሚጠመዱ በአካል በተገኙበት ቦታ የሚካሔደውን ነገር ከልብ አትከታተሉም ሲባሉ እንከታተላለን መሳተፍም እንችላለን ብለው እንደሚከራከሩ ይገልጻሉ፡፡ ነገር ግን በአንድ ጊዜ ሁለትና ከዚያ በላይ ነገሮችን ለማድረግ መሞከር አስቸጋሪ እንደሆነ የተረጋገጠ ነው፡፡
‹‹ሰው ትልቅ ጉዳይ ለማዋየት ቀጥራቸው እንኳ አሁንም አሁንም ስልካቸውን ከመመልከት የማይቦዝኑ አሉ፡፡ መነጋገር የሚያምረው ዓይን ዓይን እየተያዩ ነው፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ሰው እንዴት ማውራቱን ሊቀጥል ይችላል? እኔ ከእንደዚህ ዓይነት ሰው ጋር ለመቀጣጠርም ፍላጐት የለኝም›› ይላሉ፡፡
እንደ እሳቸው እምነት የዚህ ዓይነቱ የሰዎች በሞባይል ስልክ መጠመድ ቤተሰባዊ፣ ማኅበራዊ ግንኙነት እንዲሁም ጓደኝነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ሰዎች ትኩረት ሰጥተው ሊከውኑት የሚገባውን ነገር በአግባቡ እንዳይከውኑ ስለሚያደርግ ውጤታማነትን በጣም ይቀንሳል፡፡
ምንም እንኳ ዘወትር ሞባይል ስልክ ላይ የመጠመድ ነገር በታዳጊዎች ላይ የሚያይል ቢሆንም የተማሩና የተረጋጉ በሚሏቸው ጐልማሶች ላይ መታዘባቸውን በመጥቀስ ችግሩ አሳሳቢ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ከብዙ ነገሮች አንፃር ስልክ በስልክ አይጠመዱም የሚባሉ ሰዎች እንኳ ከስልካችን አንለይ ያሉበት ጊዜ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡
‹‹ሁሌም ስልክ ላይ መሆን ዘመን የተሻገሩ የማኅበራዊ እሴቶችን ይሸረሽራል፡፡ አሁን ያለው ሁኔታ ሰዎች መቼ ነው ከስልክ ከኢንተርኔት ዓለም ውይይታቸው ራሳቸውን ገትተው በአካል በተገኙበት ቦታ ወዳሉ ሰዎች ትኩረታቸውን የሚመልሱት?›› ሲሉ በመጨረሻ ጥያቄአቸውን ይሠነዝራሉ፡፡
ትራፊክ ፖሊስ በማይኖርባቸው ቦታዎች ላይ ስልካቸውን እያዩ፣ መልዕክት እየመለሱና ስልክ እያነጋገሩ የሚያሽከረክሩ ጥቂት እንዳልሆኑ በአዲስ አበባ ትራፊክ ፖሊስ ሕዝ ግንኙነት ኢንስፔክተር አሰፋ መዝገቡ ይገልጻሉ፡፡ አስረግጦ ለመናገር ጥናት የሚያስፈልግ ቢሆንም በተደጋጋሚ ከሚታዩ አጋጣሚዎች በመነሳት በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ በስልክ ምክንያት የሚደርሱ የትራፊክ አደጋዎች ጥቂት እንደማይሆኑም ይገምታሉ፡፡
በዘንድሮው የፈረንጆች ዓመት አሜሪካ ውስጥ የተሠራ ጥናት እንደሚያሳየው በጥናቱ ከተካተቱ 77 በመቶ የሚሆኑት መንገድ ላይ እየሔዱ በማንኛውም መንገድ ስልካቸውን መጠቀም ችግር የለውም ብለው የሚያስቡ ሲሆን፣ ሦስት አራተኛ የሚሆኑት መደብር ውስጥ ተሰልፈው ወይም በሕዝብ መተላለፊያዎች ስልካቸውን መጠቀማቸው ችግር እንደሌለው ያምናሉ፡፡ ከ88 በመቶ በላይ የሚሆኑት ቤተሰብ ተሰብስቦ እራት እየበላ፣ ስብሰባ ላይ፣ በፊልም ወይም በቴአትር አዳራሽ እንዲሁም በአምልኮ ቦታ ስልክ መጠቀም ተገቢ አይደለም ብለው የሚያምኑ ቢሆንም ተግባራቸው ግን በተቃራኒው መሆኑን ጥናቱ ያሳያል፡፡
የሰዎች ሁልጊዜም ስማርት ፎናቸውን ኦን ማድረግና ስልካቸውን ሳይመለከቱ ደቂቃዎች እንዲያልፉ አለመፈለግ ከፍተኛ ችግር እየሆነ መሆኑን ጥናቱ ይደመድማል፡፡ የመደምደሚያው መሠረት የሰዎች በእውነተኛው ዓለም ከጐናቸው ከተቀመጠ ሰው ይልቅ ትኩረታቸው በስልክ ሲያዝና ፍላጐታቸው በአካል አብሯቸው ካልሆነ ሰው ጋር መነጋገር መሆን መሠረታዊ የሰው ልጆችን የግንኙነት ዘዬ ይረብሻል የሚል ነው፡፡ በጥናቱ የተጠቀሰው ሌላው ችግር ደግሞ አጠገብ ካለ ሰው ይልቅ በስልክ የመጠመድ ነገር በፊት በፊት ይተች የነበረ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ተቀባይነት እያገኘና እንደ መደበኛ ነገር እየተቆጠረ ብዙዎችም እዚህ መስመር ውስጥ እየገቡ መሆኑ ነው፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሶሺዮሎጂ ዲፓርትመንት መምህር የሆኑት ተባባሪ ፕሮፌሰር ኢዛና ዐምደወርቅ በሞባይል ስልክ የመጠመድ ነገር በስፋት እየታየ መሆኑን ይህም በራሳቸው ዋጋ ያላቸውን ማኅበራዊ ግንኙነቶችን እየረበሸ ሰዎችን ወደ አርቴፊሻል ግንኙነቶች እያሻገረ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡
ቀን በትምህርትና በሥራ ተወጥረው የማይገናኙና የማይተያዩ የአንድ ቤተሰብ አባላት ምሽት ላይ ለግማሽ ወይም ለአንድ ሰዓት ራት ላይ ሲገናኙ እንኳ ስልካቸውን ለመተው አለመፈለግ የችግሩን ስፋት እንደሚያሳይ ይገልጻሉ፡፡ ‹‹ተለምነው እራት የሚበሉም አሉ፡፡ በሕይወታቸው ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ ካላቸው ቤተሰቦቻቸው ይልቅ ከማያይዋቸው ሩቅ ካሉ ምናልባትም እየቆዩና በመሀል እየጠፉም ከሚመልሱላቸው ጓደኞቻቸው ጋር ቻት ማድረግን የሚመርጡ ብዙዎች ናቸው፡፡ ይህ የኢንተርኔት ግንኙነት በብዙ መልኩ እውነተኛውን ግንኙነት አይስተካከለውም አርቴፊሻል ነው፡፡›› ይላሉ፡፡
በስልክ መጠመድ እንደ አዲስ አበባ ባሉና በሌሎች ትልልቅ ከተማዎች ብቻም ሳይሆን በትንንሽ ከተሞችም ቦታ ሳይመረጥ መማሪያ ክፍል፣ ለቅሶ ቤት፣ ሠርግ ላይ እንዲሁም ትልልቅ አገራዊ ስብሰባዎች ላይም እየተስተዋለ መሆኑን መታዘባቸውን ይናገራሉ ተባባሪ ፕሮፌሰሩ፡፡ እሳቸው እንደሚሉት ስብሰባዎች ላይ ወይም ክፍል ውስጥ ሆኖ ማኅበራዊ ድረ ገጽ ማየት ወይም የስልክ መልዕክት ማንበብም ሆነ መመለስ እንደተለመደ ነገር እየታየ መሆኑንም ይጠቁማሉ፡፡
ከጥቂት ዓመታት በፊት ምሥራቅ አፍሪካ ላይ ስማርት ፎን ይዞ መታየት የሚያኮራ ነገር ሆኖ ነበር፡፡ ነገር ግን ይህ ሁኔታ በተለይም ዝቅተኛ ዋጋ ያላቸው ስማርት ፎኖች ገበያውን በማጥለቅለቃቸው ሊቀየር ችሏል፡፡ እንደ ህዋዌ፣ ቴክኖና ዜድቲኢ ያሉ የቻይና ኩባንያዎች በዚህ ሒደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ይታወቃል፡፡ በሌላ በኩል ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ተጠቃሚዎች የሚሆኑ ስልኮችን የሚያቀርበው ሳምሰንግም በዚህ ረገድ የሚጠቀስ ነው፡፡
እየጨመረ ያለውን የሰዎችን በስማርት ፎን መጠመድ በመመልከት የተለያዩ አገሮች ለችግሩ ምላሽ እየሰጡ ነው፡፡ በኢንተርኔትና እንደ ሞባይል ባሉ ዲጂታል ቁሶች መጠመድ እንደማንኛውም ሌላ ሱስ እንዲታይ ማድረግ የመጀመሪያው ዕርምጃ ሲሆን፣ ከዚህ ሱስ ማገገቢያ ማዕከል እስከማዘጋጀት የገፉም አሉ፡፡ ለምሳሌ በሴንጋፖር በስልክ ሱስ ለተያዙ የምክር አገልግሎት ማዕከሎች አሉ፡፡ የዚህ ዓይነቱ የኢንተርኔትና የሞባይል ስልክ ሱስ እንደ አእምሯዊ ጤና መዛባት መታየት አለበት የሚል ክርክር የሚያነሱ የሥነ አእምሮ ሐኪሞችም አሉ፡፡
ቀደም ሲል ከስማርት ፎኖች ጋር በተያያዘ ጐልቶ ይታይ የነበረው ችግር በሞባይል ጌሞች መጠመድ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የማኅበራዊ ድረ ገጾች ሱስ እያየለ መምጣቱን መረጃዎች ያመለክታሉ::
ምንጭ:http://ethiopianreporter.com

‹‹የመንግሥት አመራር በሙሉ ሙስና ስለፈጸመ ስብስብ አድርጋችሁ የምታደርጉትን አድርጉ የሚል መልዕክት አልደረሰኝም››

ባለፈው ዓርብ መስከረም 7 ቀን 2008 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽነር አቶ ዓሊ ሱሌይማን፣ ከጋዜጠኞች ከተነሱላቸው ጥያቄዎች መካከል አንዱ መንግሥታዊው ሥርዓት በሙስና ውስጥ
መዘፈቁን በግልጽ እየተናገረ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ግን በመናኛ ጉዳዮች ላይ አተኩሯል የሚል ነው፡፡ የፖለቲካና የሕግ ቋንቋ የተለያዩ መሆናቸውን የተናገሩት አቶ ዓሊ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዕርምጃ የሚወስደው በማስረጃ ላይ ተመሥርቶ ነው በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ ጉባዔ ወቅት በሙስና ላይ ቁርጠኛ የሆነ አመራር አለመሰጠቱና ሙስናን መታገል አለመቻሉ ቢገለጽም፣ እከሌ ሙሰኛ ነው ተብሎ መረጃ ባለመቅረቡ ወደ ሕግ ለመሄድ አይቻልም ብለዋል፡፡ መንግሥት አሁንም ሙስናን ለመታገል ቁርጠኛ መሆኑንና እሳቸውም የተረዱት በዚህ መንገድ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ‹‹የመንግሥት አመራር በሙሉ ሙስና ስለፈጸመ ስብስብ አድርጋችሁ የምታደርጉትን አድርጉ የሚል መልዕክት አልደረሰኝም፤›› ያሉት አቶ ዓሊ፣ ከሙስና ጋር በተያያዘ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች የሰጡዋቸው ምላሾች በ ቢዝነስና ኢኮኖሚ ገጽ ላይ ተስተናግደዋል፡፡

ምንጭ:http://www.ethiopianreporter.com

ታሪክን የኋሊት

መስከረም 06፣2008
የጀርመን ናዚዎች፣ ዓለምን የመቆጣጠር ክፉ ኃሳብ ባደረባቸው ጊዜ፣ ክፉ ኃሳባቸውን ፖላንድን በመውረር አንድ ብለው ጀመሩ፡፡ አገሪቱን፣ በ20 ቀናት ሙሉ ለሙሉ፣ በመዳፋቸው አስገቧት፡፡ ፓላንዳውያን ፣አገራቸውን ከናዚዎች ወረራ ለመከላከል፣ የተቻላቸውን አደረጉ፡፡ የናዚዎች ዘመቻ፣ 16ኛ ቀኑን ባስቆጠረ ማግስት፣ ከምስራቅ አቅጣጫ፣ የቀድሞዋ ሶቪየት ህብረት ቀይ ጦር ወረራ መክፈቱ፣ ለፖላንዳውያኑ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆነባቸው፡፡ ይህ ከሆነ፣ ዛሬ ልክ 76 ኛ ዓመቱን ደፈነ፡፡ ጀርመኖቹ ወረራ በጀመሩ በ20 ቀናቸው፤ ሶቪየቶቹ በ4 ቀናት ውጊያ ፖላንድን ተቃረጧት፡፡ ሶቪየት ህብረት፣ የፖላንድን ምስራቃዊ ግዛት የያዝኩት፣ የዩክሬንና የቤሎሩሲያን ግዛቶቼን ደህንነት ለማስጠበቅ ነው፣ የሚል ምክንያት አቀረበች፡፡
እውነታው ግን፣ ፖላንድ፣ በጀርመን ናዚዎች ልትወረር አንድ ሳምንት ሲቀራት፣ በጀርመንና በቀድሞዋ ሶቪየት ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ በተፈራረሙት፣ ሚስጥራዊ ስምምነት መነሻ ነበር፡፡ ሚስጥራዊው ስምምነት፣ የዚያን ጊዜዎቹን የሁለቱን አገሮች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስም በመያዝ፣ በታሪክ የሪቨንትሮፕ ሞሎቶቭ ስምምነት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ስምምነቱ፣ ላይ ላዩን ያለመጠቃቃት ውለታ ቢመስልም፣ ሚስጥራዊ ክፍሉ የግዛት መሸንሰንና የተፅዕኖ ክልልን መፍጠርን የተመለከተ ነው፡፡ የቀድሞዋ ሶቪየት ህብረት፣ የፖላንድን ምስራቃዊ ግዛት የያዘችውና ሦስቱን የባልቲክ አገሮች ኢስቶኒያ፣ላቲቪያና ሊትዌንያን ወደ ራሷ የቀላቀለችው፣ በዚሁ ሚስጥራዊ ስምምነት መነሻ ነው ይባላል፡፡ የሶቪየት ህብረትና የናዚዎቹ ያለ መጠቃቃት ውለታም ሆነ፣ ሚስጥራዊው ስምምነት፣ ብዙ ርቀት አልተጓዘም፡፡ የጀርመን ናዚዎች፣ ስምምነቱን ሶቪየት ህብረትን ለማዘናጋት ተጠቅመውበታል፡፡ ናዚዎቹ አቅማቸው መፈርጠሙ በተሰማቸው ጊዜ፣ ከሞስኮ ጋር የገቡትን ያለመጠቃቃት ውለታ አሸቀንጥረው ጣሉት፡፡ ሁለት ዓመት ባልሞላ ጊዜ፣ ናዚ ጀርመን ሶቪየት ህብረትን ወረረች፡፡ ወረራው የቀድሞዋን ሶቪየት ህብረት በጦርነቱ ከተሳተፉ አገሮች ሁሉ፣ የላቀውን ዋጋ አስከፈላት፡፡ የ2ኛው የዓለም ጦርነት፣ ዋነኛዋ ቀንበር ተሸካሚ ሆነች፡፡ ሌላ ሌላው፣ ጥፋትና ውድመት፣ ወደ ጐን ቢባል እንኳ ፣ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጐቿን ሕይወት አስገብሯታል፡፡

ምንጭ:shegerfm.com

ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ፣ አለምን እየመራ ነው አዲስ አልበሙ፣ በሳምንት 412 ሺህ ኮፒ ተሽጦለታል

“ዘ ዊኪንድ” በሚል ቅፅል ስሙ የሚታወቀው ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ፣ ባለፈው ሳምንት በአለም ደረጃ በቢልቦርድ ምርጥ አልበሞችሰንጠረዥ የ1ኛነትን ደረጃ በዚህ ሳምንትም አለምን እየመራ ይቀጥላል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተዘገበ፡፡“ቢዩቲ ቢሃይንድ ዘ ማድነስ” የተሰኘው አዲሱ የአቤል አልበም፣ ለገበያ በቀረበበት የመጀመሪያው ሳምንት በሽያጭ ብዛት መሪነቱን እንደሚይዝ ተገምቶ የነበረ ቢሆንም፣ ከተገመተው በላይ እንደተሳካለት ፎርብስ ዘግቧል፡፡ በ350 ሺህ የአልበም ሽያጭ አንደኛ እንደሚሆን የተገመተው የአቤል አልበም፣በ412 ሺህ ያህል ተቸብችቧል፡፡ በአዲሱ አልበሙ ውስጥ የተካተቱት 12 ሙዚቃዎችም በያዝነው ሳምንት የቢልቦርድ 50 ምርጥ ሙዚቃዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተዋል፡፡ካለፉት ሰባት አመታት ወዲህ፣ በቢልቦርድ የምርጥ ዘፈኖች ሰንጠረዥ፣ በአንድሳምንት ሁለት ዘፈኖቹ፣ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ባለው ደረጃ ውስጥየተካተቱለት የመጀመሪያው ወንድ ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ ብቻ መሆኑን ቢል ቦርድ ገልጿል የሰሞኑን የአቤል ስኬት ሲዘግብም፤ በ57 አመታት የቢልቦርድ ሰንጠረዥ ታሪክ፣ አቤል በአንድ ሳምንት ውስጥ ብዙ ዘፈኖቹ፣ በምርጥ 100 ዘፈኖች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱለት ስድስተኛው ድምጻዊ ነው ብሏል፡፡ ዘንድሮ፣ በአንድ ሳምንት ውስጥ፣ ከአቤል የአልበም ሽያጭ የሚበልጥ ሪከርድ ያስመዘገበ ድምፃዊ የለም ከድሬክ በስተቀር፡፡ አመቱ የአቤል ተስፋዬ ነው ያለው ፎርብስ መጽሄት፤ የድምጻዊው የሙዚቃ ስራዎች የካናዳንና የአሜሪካን ሬዲዮ ጣቢዎች በስፋት መቆጣጠራቸውንና ከፍተኛ ተወዳጅነት ማትረፋቸውን ዘግቧል፡፡ የአቤል ዘፈን በአሜሪካ ሬዲዮ ጣቢያዎች በብዛት በመሰራጨት አቻ አልተገኘላትም፡፡ “ስድ” ቃላትን በሙዚቃዎቹ ውስጥ ይደጋግማል በሚል ትችት የሚሰነዘርበት አቤል ተስፋዬ፤ በሙዚቃዎቹ ኢትዮጵያዊኛ ቃና ይንፀባረቃል የሚለው አስተያየት ከሁሉም በላይ እንደሚያስደስተው ገልጿል፡፡ በዘፈን መሃልም አልፎ አልፎ አማርኛ ያስገባል፡፡

Friday, September 4, 2015

Your brand new phone could still have malware



A new phone is supposed to be a clean slate. But alarmingly, that's not always the case.
Security company G Data has identified more than 20 mobile phones that have malware installed despite being marketed as new, according to a research report. And it doesn't appear the infection is occurring during manufacturing.
"Somebody is unlocking the phone and putting the malware on there and relocking the phone," said Andy Hayter, security evangelist for G Data.
Many of the suspect phones are sold in Asia and Europe through third parties or middleman and aren't coming directly from the manufacturers, Hayter said.
Brands of affected phones include Xiaomi, Huawei, Lenovo, Alps, ConCorde, DJC, Sesonn and Xido.
G Data has contacted some manufacturers, including Lenovo, whose S860 Android smartphone in one instance was found to have the malware.
Ray Gorman, Lenovo's executive director of external communications, wrote in an email that the device G Data analyzed came from a third-party marketplace. The malware was installed by middlemen, he wrote.
"This is the only such occurrence we have been made aware of," Gorman wrote. "We always recommend customers transact with authorized distribution channels and only accept merchandise that comes in an official box with original factory seals."
The malware is embedded in a legitimate app, such as Facebook, which is sometimes preinstalled on phones, Hayter said. It can read and send text messages, install other apps, collect and change call data, grab location information, record phone calls or send premium SMSes, according to G Data's report.
It's impossible for consumers to remove since it resides inside the phone's firmware.
"You can't take it off there unless you unlock the phone," Hayter said.
G Data was alerted to the problem after receiving support calls from users who said a file had been quarantined but that it couldn't be removed.
The problem has been around for a while. In June 2014, G Data said it found malware in the firmware of a relatively inexpensive Android device made by the Chinese manufacturer Star.
The company's analysts bought Star's N9500 and found malware that purported to be an app for Google's Play Store. The malware, they found, could not be deleted.
In early 2014, Marble Security found malware embedded within Netflix's app that had been preinstalled on six mobile devices made by Samsung Electronics.
That malware grabbed credit card information and passwords and sent it to a server in Russia.

Thursday, August 27, 2015

High-Tech 'Smart' Cane Helps Blind People Recognize Faces


A new, high-tech cane for the blind is designed to recognize the faces of the person's friends and family members.
Using smartphone technology, the device — known as the "XploR" mobility cane — can identify faces from up to about 33 feet (10 meters) away, researchers say.
If the cane recognizes someone, it alerts a visually impaired user by vibrating and transmitting a sound signal. The cane is also equipped with GPS to help the user navigate. [Bionic Humans: Top 10 Technologies]

"My grandfather is blindand I know how useful this device could be for him," Steve Adigbo, one of the cane's developers and a student at Birmingham City University in England, said in a statement, adding,"There’s nothing else out there like this at the moment."
The cane works by taking pictures of people in the environment and comparing them to a bank of images stored on an internal memory card, using facial-recognition software. When it finds a match, it produces a vibration and sends a signal to an earpiece via Bluetooth, the researchers said.
The team conducted market research at the Beacon Centre for the Blind in the British town of Wolverhampton, and found that in addition to high-tech features, the cane needed to be lightweight and easy to use.
The researchers have already presented the cane to medical professionals and scientists in Luxembourg and France, and plan to take their device to Germany later this year. They also plan to return to Beacon to test the product and show off its training and security features.
Meanwhile, American researchers have been developing a vibrating vest that uses a variety of sensors to help blind people navigate. The device, dubbed Eyeronman and developed by New York-based company Tactile Navigation Tools, could also help soldiers, firefighters and others in poor visual conditions, researchers say.

Wednesday, July 15, 2015

ተዋናይት-ቤዛዊት-መስፍን-በእስራት-ተቀጣች

አዲስ አበባ፣ ሀምሌ 8፣ 2007 (ኤፍ. ቢ. ሲ) በተለያዩ ፊልሞችና የቴሌቪዥን ድራማዎች ላይ በመተወን የምትታወቀው ተዋናይት ቤዛዊት መስፍን እና ግብረ አበሯ በእስራት ተቀጡ።
በአዲስ አበባ ከተማ በኮልፌ ቀራንዮ ነዋሪ የሆኑት ተከሳሾቹ በእስራት የተቀጡት ከታዘዘላቸው ውጭ ተጨማሪ ገንዘብ ከባንክ ቤት በማውጣት ለግል ጥቅማቸው በማዋላቸው ነው።
የ22 አመቷ ተዋናይት ከግብረ አበሯ ጋር በመሆን በተሰጣቸው የ4 ሺህ ብር ቼክ ላይ ከፊት ለፊቱ ሁለት ቁጥርን በመጨመር ያልተፈቀደላቸውን 24 ሺህ ብር ከወጋገን ባንክ ሰባራ ባቡር ቅርንጫፍ አውጥተዋል።
ተከሳሾቹ ለአቶ ዮናታን ባልቻ መኪና በማከራየት የኪራይ ስምምነት ውል ያላቸው ሲሆን፥ በውላቸው መሰረትም ሚያዚያ 8 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 2 ሰአት አካባቢ የ4 ሺህ ብር ቼክ ተቀብለዋል።
ግለሰቦቹ ሚያዚያ 12 ቀን 2005 ዓ.ም ላይም ከመኪና ተከራዩ አቶ ዮናታን በተቀበሉት የ4 ሺህ ብር ቼክ ላይ ከፊት ለፊቱ 2 ቁጥርን በመጨመር ተጨማሪ 20 ሺህ ብር ከባንክ ቤቱ አውጥተዋል።
በዚህም መሰረት የፌደራሉ አቃቤ ህግ ተከሳሾቹ የማይገባቸውን ብልጽግና ለማግኘት በማሰብ በፈፀሙት ወንጀል ክስ በመመስረት የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን አቅርቧል።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 5ኛ የወንጀል ችሎትም ተከሳሾቹ የወንጀል ድርጊቱን ማስተባበል ባለመቻላቸው ጥፋተኛ ብሏቸዋል ።
ተከሳሾቹ ወንጀሉን በስምምነት በማበር የፈፀሙት በመሆኑ ቅጣቱ ከፍ ብሎ እንዲወሰን አቃቤ ህግ የቅጣት ማክበጃ አቅርቧል።  
ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ተከሳሾቹ ያላቸውን የቅጣት ማቅለያ እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
በዚህም 1ኛ ተከሳሽ ቤዛዊት መስፍን የዕድሜዋን ወጣትነት፣ ከዚህ ቀደም በምንም አይነት የወንጀል ድርጊት አለመሳተፏንና የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆኗን በቅጣት ማቅለያነት አቅርባለች።
2ኛ ተከሳሽ አቶ ነቢል ይማም ምንም አይነት የቅጣት ማቅለያዎችን አላቀረበም።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 5ኛ የወንጀል ችሎትም 1ኛ ተከሳሽን በ6 ወር ቀላል እስራትና በ1 ሺህ 500 ብር እንዲሁም 2ኛ ተከሳሽን በ1 አመት ከ6 ወር እና በ3 ሺህ ብር እንዲቀጡ ወስኗል።
ምንጭ:— FBC